ስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ያለንን ሙያዊ አቅም የሚያጎለብትና ክፍተቶቻችንን በመለየት በቀጣይ የተሻለ ስራ መስራት እንድንችል አጋዥ ነው - ሰልጣኞች። ስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ያለንን ሙያዊ አቅም የሚያጎለብትና ክፍተቶቻችንን በመለየት በቀጣይ የተሻለ ስራ መስራት እንድንችል የሚያደርግ ነው ሲሉ ሰልጣኞች ተናገሩ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከክልልሉ ከሁሉም ዞኖች፤ ልዩ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም…
"የሀዲያ ዞንን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ማዕከል እናደርጋለን" - በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ 2ኛ ዙር ዞናዊ የምርምርና ፈጠራ ስራዎች ኤግዚብሽንና አውደ ርዕይ በሀዲያ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ፣ ትምህርት መምሪያ እና ሥራ ዕድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዝ መምሪያ በጋራ የተዘጋጀ መድረክ ተካሄዷል፤ ሆሳዕና፡ ግንቦት 8/2017 ዓ.ም በአውደ ርዕዩ መክፈቻም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ም/ኃላፊና የሳይንስ ፈጠራ…
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ጉልህ ስኬቶች ተመዝግበዋል - ፕሬዚዳንት ታዬ። ባለፉት ዓመታት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ጉልህ ስኬቶች መመዝገባቸውን ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ ÷ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የቴክኖሎጂ ኤክስፖ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሸን ማዕከል በይፋ ከፍተዋል። በመክፈቻ ንግግራቸውም ባለፉት ዓመታት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች…
በዞኑ የማህበረሰቡን ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎች በመደገፍና በማብቃት ለታለመላቸው አላማ እንዲውሉ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ አሳሰቡ። በጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ትምህርት መምሪያ በጋራ በመሆን "ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለሁለንተናዊ ሃገር ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የነበረው 4ኛ ዙር ዞን አቀፍ የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽንና ውድድር ተጠናቀቀ። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ…
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከክልልሉ ከሁሉም ዞኖች፤ ልዩ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከተለያዩ ተቋማት ለተውጣቱ የኢኮቴ ከፍተኛ ባለሙያዎች በልዩ ልዩ የሙያ ዘርፎች የአድቫንስድ ቴክኒካል ስልጠና መስጠት ጀመረ። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ፤ በቢሮ ማሽን ጥገናና ዕድሳት፣ በኔትወርክ ልማትና አስተዳደር እና በሶፍትዌር ልማት ማበልጸግ ዙሪያ በወራቤ ከተማ መስጠት…
የዜጎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ በነጻ የቀረበው የኮደርስ ስልጠና (ሆሳዕና፣ ግንቦት 4፣ 2017) የዜጎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ኢትዮጵያ በነጻ እንዲቀርብ ያደረገችው የኮደርስ ስልጠና ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚጠይቅ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አማካሪ አብዮት ባዩ (ዶ/ር) አስገነዘቡ፡፡ የ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደሮች ፕሮግራም ወጣቶች የዲጂታል ክህሎት ኖሯቸው በዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ያስችላል…
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በሀላባ ዞን''የዘመነ ዲጂታል ኢኮኖሚ የዕድገታችን መሰረት ነው''በሚል መሪ ቃል የሀላባ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ከት/ት መምሪያ ጋር በመሆን የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ውድድር፣ባዛር፣ኤግዚቢሽን እና ፓናል ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። መድረኩ በሀላባ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ በአቶ መሀመድ ሀሰን እና በአቶ አበበ አልዬ የሀላባ ዞን አስተዳደር ማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ እየተመራ ነው። በመድረኩ ላይም…
መሶብ የሁለተኛው ምዕራፍ የሀገር በቀል ሪፎርማችን አንዱ መሠረት ነው፡፡ የመንግስትን የመፈጸም አቅምን ለማሳደግ፣ ለማፋጠን ብሎም የተቋማት ግንባታን ለማጠናከር ማዕከሉ ትልቅ አቅምን ይፈጥራል፡፡ ለዓመታት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት በመንግስት በኩል ለሚደረገው ጥረትም ወሳኝ እርምጃ ነው። መሶብ ውብና ምቹ የሥራ ከባቢ፣ ሀገር በቀል የአገልግሎት ማሳለጫ የቴክኖሎጂ ስርዓትን ያሟላ እንዲሁም ሙያዊ እውቀትና ክህሎትን በተላበሱ ወጣት አገልጋዮች…
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሰራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው። ለዚህ ቁርጠኝነታቸን አንዱ ማሳያ የሆነውን የመሶብ የአንድ መስኮት አገልግሎት ማዕከልን ዛሬ መርቀናል። ይኽን አዲስ ማዕከል የሚገልጡ ሶስት ቁልፍ አላባውያን አሉ። የቆየ እና የተጎዳ ህንፃን ወደ ዘመናዊ እና ሥነውበታዊ ደረጃው ለሥራ ከባቢ አስደሳች ወደ ሆነ ህንፃ መለወጡ አንዱ ነው። አገልግሎቶችን…
በክልሉ ሁሉም ተቋማት ወረቀት አልባ አገልግሎት ለማቅረብ በሚያችላቸው ሲስተም ዝርጋታ ላይ ልዩ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። (ሆሳዕና፣ ሚያዚያ 17/2017)፣ የቢሮው የ9 ወራት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው። በክልሉ ሁሉም የመንግስት ተቋማት ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ አገልግሎት ለማቅረብ በሚያችላቸው የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሲስተም ዝርጋታ ላይ ልዩ ትኩረት አድርጎ እየሰራ…