የቢሮዉ ኃላፊ መልዕክት

message

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ቢሮ

                       አቶ ሰላሙ አመዶ ዋጨንጎ የቢሮው ሀላፊ መልዕክት                  

የቢሮው ሀላፊ መልዕክት

ሳይንስና ኢንፎርመሽን ቴክኖሎጂ   ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማኀበራዊና ፖለቲካዊ ዕድገት የሚያበረክተው  አስተዋጽኦ ከምንም በላይ መሆኑን ዛሬ ላይ የስልጣኔ ጫፍ የደረሱ፣ የበለፀጉና የዓለማችን ሃያላን ተብለው የሚጠሩ አገሮች ምሥክሮች ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ መንግስት የሀገራችን ሕዝብ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆንና የቴክኖሎጂው ሽግግር ከጫፍ እንዲደርስ ተግቶ በመሥራቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀላል የማይባል የሀገራችን ሕዝብ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡  ለዚህም ማሳያ መሆን የሚችሉ በርካታ ተግባራትን መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በክልላችን የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከሚመለከታቸው /ቤቶች ጋር በመሆን በአያሌ የገጠር ቀበሌያትና ወረዳዎች የገጠሩ ሕብረተሰብ ከተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከሌሎች የመረጃ ምንጮች የሚፈልጓቸውን መረጃዎች በተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አማካይነት ማግኘት እንዲችሉ የማህበረሰብ መረጃ ማዕከላትን አቋቁሞ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡  ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሽቦ አልባ ስልኮችም በብዙ የገጠር ቀበሌያት በቢሮውና አግባብነት ባላቸው ተቋማት በኩል የተሠራጩ ሲሆን እስኩል ኔትና ወረዳ ኔቶችም እንዲሁ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ  በክልል ማዕከል፣ በዞኖች፤ በልዩ ወረዳዎች፤ በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ  መሠረተ ልማት ደረጃ በደረጃ እየተዘረጋ ያለ ሲሆን በዋናነት የመንግስት መረጃ ሥርዓት  የማሳለጥ፣ የቪዲዮ ኮንፍረንስ አገልግሎት በመስጠት ፈጣን የሆነ መረጃ እንዲዳረስ የማድረግና የማህበረሰብ መረጃና ሬድዮ አገልግሎት በመስጠት በርካታ ወጣቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን ወደ ስራ እያስገባ ይገኛል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢኮቴ ዘርፍ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተመራቂዎችን በማህበር በማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ማለትም ስልጠና፣ የገበያ ማፈላለግና የማማከር አገልግሎት በመስጠት የግል ካምፓኒ ፈጥረው  ወደ ንግድ ዓለም እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቢሮውን ዌብ ሳይት በማልማት እና የፌስቡክ ገጽ በመክፈት እንዲሁም የተለያዩ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በተቋማችን አጠቃላይ አፈጻጸምና ሁኔታ ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እተከናወነ ይገኛል፡፡

ወቅታዊ ዜናዎች

zena51

የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይዎች ወጣቶች እርስ በርስ እንዲማማሩ ጠቃሚ ልምድ የሚፈጥሩ ናቸው ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይዎች ወጣቶች እርስ በርስ እንዲማማሩ ጠቃሚ ልምድ የሚፈጥሩ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር…

zena51

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት 2ኛ ዙር ክልላዊ የሳይንስና የፈጠራ ሰራዎች ዐውደ- ርዕይ እና ውድድር ተከፈተ። በክልሉ እየተካሄደ የሚገኘውን የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ እና ውድድር የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ እና አፈ ጉባኤ ፋጤ ሰርሞሎ በወልቂጤ…

zena50

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 2ኛ ዙር ክልላዊ የሳይንስና የፈጠራ ስራዎች ዐውደ_ርዕይ እና ውድድር ሰኔ 12 እና 13 በወልቂጤ ከተማ ይካሄዳል። "ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሳይንስ፣ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ቃል ነው የሚካሄደው። 2ኛውን ዙር ክልላዊ የሳይንስና የፈጠራ ስራዎች…

zena49

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአፍሪካ ህጻናት ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ በወራቤ ከተማ በህጻናት የተዘጋጀ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ተከፈተ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሐመድ ናስር እና የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ አውደ…

zena50

አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመተግበርና በማስፋት ወቅቱን የሚመጥን ዲጂታል ተቋም ለመገንባት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በዛሬው እለት በዲጂታል ሌተሪንግ ሲስተም አተገባበር ላይ በወራቤ ከተማ ለጠቅላላ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል። ‎ ‎…

zena49

ክልሉ በቱሪዝም ዘርፍ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ለማስተዋወቅ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዌብሳይት ፋይዳው የጎላ እንደሚሆን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል መንገሻ ክልሉ በቱሪዝም ዘርፍ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ለማስተዋወቅ የዲጂታል…

ተልዕኮ

ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋት ክልላዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነዉ፡፡

ራዕይ

“በ2030 በክልላችን ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣ የማልማት፤ የመፍጠር፣ የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት”      

እሴቶች

በጎ ህሊናና ቅን ልቦና፣

የስራ ፍቅርና ትጋት፣

ያልተገደበ አስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣

ለለውጥ በጋራ መስራት፤

ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤

ችግር ፈቺነት፤

የማይረካ የመማር ጥማት፤

ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣

ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣