የቢሮዉ ኃላፊ መልዕክት

message

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ቢሮ

                       አቶ ሰላሙ አመዶ ዋጨንጎ የቢሮው ሀላፊ መልዕክት                  

የቢሮው ሀላፊ መልዕክት

ሳይንስና ኢንፎርመሽን ቴክኖሎጂ   ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማኀበራዊና ፖለቲካዊ ዕድገት የሚያበረክተው  አስተዋጽኦ ከምንም በላይ መሆኑን ዛሬ ላይ የስልጣኔ ጫፍ የደረሱ፣ የበለፀጉና የዓለማችን ሃያላን ተብለው የሚጠሩ አገሮች ምሥክሮች ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ መንግስት የሀገራችን ሕዝብ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆንና የቴክኖሎጂው ሽግግር ከጫፍ እንዲደርስ ተግቶ በመሥራቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀላል የማይባል የሀገራችን ሕዝብ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡  ለዚህም ማሳያ መሆን የሚችሉ በርካታ ተግባራትን መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በክልላችን የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከሚመለከታቸው /ቤቶች ጋር በመሆን በአያሌ የገጠር ቀበሌያትና ወረዳዎች የገጠሩ ሕብረተሰብ ከተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከሌሎች የመረጃ ምንጮች የሚፈልጓቸውን መረጃዎች በተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አማካይነት ማግኘት እንዲችሉ የማህበረሰብ መረጃ ማዕከላትን አቋቁሞ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡  ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሽቦ አልባ ስልኮችም በብዙ የገጠር ቀበሌያት በቢሮውና አግባብነት ባላቸው ተቋማት በኩል የተሠራጩ ሲሆን እስኩል ኔትና ወረዳ ኔቶችም እንዲሁ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ  በክልል ማዕከል፣ በዞኖች፤ በልዩ ወረዳዎች፤ በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ  መሠረተ ልማት ደረጃ በደረጃ እየተዘረጋ ያለ ሲሆን በዋናነት የመንግስት መረጃ ሥርዓት  የማሳለጥ፣ የቪዲዮ ኮንፍረንስ አገልግሎት በመስጠት ፈጣን የሆነ መረጃ እንዲዳረስ የማድረግና የማህበረሰብ መረጃና ሬድዮ አገልግሎት በመስጠት በርካታ ወጣቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን ወደ ስራ እያስገባ ይገኛል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢኮቴ ዘርፍ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተመራቂዎችን በማህበር በማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ማለትም ስልጠና፣ የገበያ ማፈላለግና የማማከር አገልግሎት በመስጠት የግል ካምፓኒ ፈጥረው  ወደ ንግድ ዓለም እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቢሮውን ዌብ ሳይት በማልማት እና የፌስቡክ ገጽ በመክፈት እንዲሁም የተለያዩ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በተቋማችን አጠቃላይ አፈጻጸምና ሁኔታ ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እተከናወነ ይገኛል፡፡

ወቅታዊ ዜናዎች

zena62

በጉራጌ ዞን የሚገኙ ወጣቶች በአዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራ ላይ የተሻለ ክህሎት እንዳላቸውና ይህንን ወደ ውጤት በመቀየር የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላቶች በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። ጉራጌ ዞን የሳይንስ ፣የኢኖቬሽን እና የቴክኖሎጂ…

zena62

የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ አስመልክቶ በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ህዝባዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው። ወራቤ፣ መስከረም 8/2018 (ስልጤ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን) ከስልጤ ዞን የተለያዩ አከባቢዎች የተውጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉበትና በህብረት ችለናል በሚል መሪ ቃል የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ…

zena63

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሁሉም ኢትዮጵያዊ ተሳትፎና በራስ አቅም የተገነባ የህብረት ተምሳሌት ነው (መስከረም 5/2017) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበራዊ ክላስተር ተቋማት ታላቁ የህዳሴ ግድብ ምረቃን አስመልክቶ "እመርታና ማንሠራራት" በሚል ሀሳብ ፓናል ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። የክልሉ ጤና ቢሮ…

zena61

የሳይበር ጥቃት መከላከል ወትሮ ዝግጁነት በማረጋገጥ ረገድ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ። ስኬታማ እና ዘላቂ የሳይበር መከላከል ወትሮ ዝግጁነት በማረጋገጥ ረገድ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ሀገራዊ የሳይበር ጥቃት መከላከል ወትሮ ዝግጁነት ላይ…

zena59

የዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎቶች አጠቃቀምንና አቅርቦትን በማሳደግ ከወረቀት ነጻ የሆኑ አገልግሎቶችን መስጠት ላይ የተጀመረውን ስራ ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸሙን እና የ2018 በጀት አመት ዕቅድን በወራቤ ከተማ ገምግሟል። የክልሉ…

zenaq58

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2017 በጀት አመት ከ72,400 በላይ ዜጎች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው ተገለጸ። የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸሙን እና የ2018 በጀት አመት ዕቅድን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና…

ተልዕኮ

ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋት ክልላዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነዉ፡፡

ራዕይ

“በ2030 በክልላችን ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣ የማልማት፤ የመፍጠር፣ የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት”      

እሴቶች

በጎ ህሊናና ቅን ልቦና፣

የስራ ፍቅርና ትጋት፣

ያልተገደበ አስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣

ለለውጥ በጋራ መስራት፤

ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤

ችግር ፈቺነት፤

የማይረካ የመማር ጥማት፤

ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣

ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣